የልደታ ክ/ከተማ ህብረት ስራ ጽ/ቤት

የልደታ ክ/ከተማ ህብረት ስራ ጽ/ቤት

የጽ/ቤቱ ኃላፊ መልእክት

ማገልገል ክብር ነው! እኛም እናንተን ዝቅ ብለን ስናገለግል ታላቅ ደስታና ክብር ይሰማናል፡፡

ጽ/ቤቱ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች የተቀመጡት ቅድመ ሁኔታዎችን ሲታሟሉ አገልግሎቶቹን በተቀመጠላቸው ስታንዳርድ መሰረት ያለምንም እንግልት የመገልገል መብት ያላችሁ ሲሆን እኛም እናንተን በደንብና መመሪያው እና በተሰጠን ስልጣንና ሃላፊነት መሰረት የማገልገል ግዴታ ያለብን ሲሆን በዚህ ሰነድ የተቀመጡትን አገልግሎቶች ለማግኘት ምንም እንቅፋት ቢገጥማችሁ ችግራችሁን ለመፍታትና ችግሩን የፈጠሩ አካላትን በአሰራርና በህግ አግባብ ለመጠየቅ ዝግጁ መሆናችንንና ሁልጊዜም እናንተን ለማገልገል ልችን ፤ጆሮአችን ፤ ህሊናችን እና ቢሮአችን ክፍት መሆኑን ልንገልፅላችሁ እወዳለሁ፡፡ ... ተጨማሪ ያንብቡ

ባዬ ባይሌ , የህብረት ስራ ጽ/ቤት ኃላፊ
image description

የጽ/ቤቱ ቡድን መሪዎች

ወ/ሮ በላይነሽ ገብሬ

የግብይት ቡድን መሪ

ዳግም ካሳ

የፋይናንስ ኅብረት ሥራ ልማት ቡድን መሪ

ወ/ሮ ፀሐይ ለማ

የህግ ቡድን መሪ

ወ/ሮ ቢሊሴ አበራ

የማኅበራት ማደራጃ ቡድን መሪ

አቶ ሄኖክ ዘዉዱ

የኢንስፔክሽንና ብቃት ምዘና ቡድን መሪ

አቶ ሥራዬ ለወየሁ

የህብረት ሥራ ኦዲት ቡድን መሪ

የልደታ ክ/ከተማ ህብረት ስራ ጽ/ቤት

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የልደታ ክ/ከተማ የህብረት ስራ ጽ/ቤት ከተሰጠው ተግባርና ኃላፊነት መነሻ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትና የለውጥ ሥራዎችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ በብቃቱና እና በሥነ-ምግባሩ የተመሰገነ የሰው ኃይል እንዲመራ በማድረግ ለተገልጋዮቹ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች በአዲስ መልክ በመለየት አደራጅቷል፡፡

በተጨማሪም በጽ/ቤት የሚሰጠው አገልግሎት የተገልጋይ ፍላጎትን ማዕከል አድርጎ ይበልጥ ተደራሽ እንዲሆን ለማስቻል የሚሰጡ የአገልግሎት አይነቶች፣ አገልግሎቱ የሚሰጥበት ስታንዳርድ፣ የሚሰጥበትን ቦታ እና ከተገልጋይ የሚጠበቁ ቅድመ ሁኔታዎችን በግልጽ በዝርዝር በማስቀመጥ የጽ/ቤቱ ሠራተኞች በተቀመጠላቸው ስታንዳርድ መሰረት ፍህታዊና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጡና ተገልጋዮች ምን ዓይነት አገልግሎት በምን ዓይነት ደረጃ ማግኘት እንደሚገባቸው ግንዛቤ በመፍጠር በዚህም ግልፅነትና ተጠያቂነት እንዲኖር፣ በህዝብና መንግስት መካከል መተማመን እንዲፈጠር፣ ልማትና ዲሞክራሲ እንዲያብብ ትልቅ አስተዋጽኦ አላቸው፡፡ በመሆኑም የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂት ለመፍታት በምናደርገው ጥረት ባለድርሻ አካላትና ህብረተሱቡ ከጽ/ቤቱ ጎን እንዲቆሙ እናሳስባለን፡፡

ጥያቄ ካልዎት እባክዎ ለመደወል አያመንቱ ወይም ይጎብኙን!!

+251912689710

አድራሻችን:-

የልደታ አስተዳደር ህንጻ 4ኛ ወለል ቢሮ ቁ 403